1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዶላር ፍለጋ፦ የኢትዮጵያ ባንኮች እና የጥቁር ገበያው ፉክክር እስከ የት ይጓዛል?

Eshete Bekeleረቡዕ፣ ነሐሴ 1 2016

ኢትዮጵያ በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሪ ተመን ሥርዓት መከተል ከጀመረች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ብሔራዊ ባንክ ባካሔደው ጨረታ አንድ ዶላር በ107 ብር ከ90 ሣንቲም ተሸጧል። ተመኑ ትላንት በባንኮች ከነበረው አማካኝ ምንዛሪ በ4 ብር ገደማ ከፍ ያለ ነው። ባንኮች በምንዛሪ ተመን ሲሽቀዳደሙ በተለምዶ ጥቁር እየተባለ የሚጠራው የትይዩ ገበያ ተዋንያን አድፍጠው ይታዘባሉ። በአዲሱ በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሪ ተመን ሥርዓት የዋጋ ግሽበት በጥር ከ30 እስከ 35 በመቶ ሊደርስ እንደሚችል የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ሰነድ ያሳያል።

https://p.dw.com/p/4jD6R
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

Äthiopien | Flughafen in Addis Abeba
ምስል Eshete Bekele/DWምስል Eshete Bekele/DW

ከኤኮኖሚው ዓለም

በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።