እምነትአፍሪቃ
የጥምቀት በዓል አከባበር በናዝሬት/አዳማ
ረቡዕ፣ ጥር 11 2014ማስታወቂያ
የ2014 ዓ.ም. የጥምቀት በዓል ዛሬ በናዝሬት/አዳማ ከተማ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች በደማቅ ኹኔታ ተከብሮ ዋለ። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ምዕመናን በታደሙበት የስርዓተ ጥምቀቱ የበዓል አከባበር በምስራቅ ሸዋ ዞን አገረ ስብከት ሊቀ-ጳጳስ ብጹእ አቡነ ጎርጎሪዮስ ቡራኬው ተከናውኖ በሃይማኖታዊ ስርዓቱ ምዕመናኑ ተጠምቀዋል። 24 ታቦታት በአንድ ላይ ካረፉበት የአዳማ መስቀል አደባባይ መንገዱን ሁሉ አጥለቅልቀው የተስተዋሉት የሃይማኖቱ ተከታዮች ታቦታቱን አጅበው ወደ እየ መንበሮቻቸው አስገብተዋልም።
ሥዩም ጌቱ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ