Negash Mohammedዓርብ፣ ግንቦት 9 2016-በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሥለ ኢትዮጵያ ፖለቲካዊና የሰብአዊ መብት ይዞታ የሰጡትን አስተያየት ኢትዮጵያ አጥብቃ ተቃወመችዉ።የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣዉ መግለጫ የአምባሳደሩን አስተያየት «ሐሰት« ና «ተቀባይነት» የሌለዉ በማለት አጣጥሎታል።-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዎላይታ ዞን ደሞዝ ያልተከፈላቸዉ የመንግስት ሠራተኞች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ያደረጉት ሰልፍ በፖሊስ ኃይል ተበተነ።-በቀጣዮቹ ሁለት ወራት 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች ወደ ሰላማዊ ሕይወታቸው ለመመለስ እቅድ መያዙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የተሃድሶ ኮምሽን አስታወቀ