Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ግንቦት 10 2016ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ማንኛውም የውጭ ሀገር የሕክምና ቀጠሮ” ከመከላከያ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል “ውጪ እንደማይፈቀድ” ተናገሩ። የኬንያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በቅርቡ ከተከሰተው ከባድ ጎርፍ ተጎጂዎችን መጠበቅ አልቻሉም፤ ቸልተኛም ነበሩ ባላቸው ሦስት ባለሥልጣናት ላይ ክስ መሠረተ። ደቡብ ሱዳን ከአንድ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ኩባንያ 13 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር መቃረቧን የተባበሩት መንግሥታት ባለሙያዎች ገለጹ። በደቡባዊ ጋዛ የምትገኘው ራፋሕ ዛሬ ቅዳሜ ከባድ ውጊያ እና የአየር ድብደባ አስተናገደች። በአፍጋኒስታን ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ ቢያንስ 68 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።