የዞን ዘጠኝ አንደኛ ዓመት የእሥር ጊዜ16 ሚያዝያ 2007ዓርብ፣ ሚያዝያ 16 2007«በሕገ መንግሥቱ እና በስርዓቱ ላይ ያነጣጠረ የአመፅ ጥሪ ለመፈፀም በሕቡዕ ተደራጅተዉ ተንቀሳቅሰዋል» በሚል ወንጀል ወህኒ የወረዱት የዞን ዘጠኝ ፀሀፍትና ጋዜጠኞች ከታሰሩ ነገ አንድ ዓመት ይሆናቸዋል።https://p.dw.com/p/1FETMምስል Fotolia/lichtmeisterማስታወቂያ ዘጠኙ ፀሐፍትና ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ወንጀል ዉስጥ የነበራቸዉ ሚና በዝርዝር እንዲቀርብ እና ክሱ እንዲሻሻል ፍርድ ቤቱ በጠየቀው መሰረት በቀጠሮ ሲታይ የቆየው ጉዳያቸው እስካሁን ውሳኔ አላገኘም ። አዲስ አበባ የሚገኘዉ ወኪላችን ዮኃንስ ገብረ እግዚአብሄር የፀሐፍቱንና የጋዜጠኞቹን ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንንን አነጋግሮ ዘገባ ልኮልናል። አዜብ ታደሰ ሒሩት መለሰ