1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ብድር 65 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል

Eshete Bekeleረቡዕ፣ ግንቦት 21 2016

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 65 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ባለፈው ሣምንት ተናግረዋል። ወደ 1.2 ትሪሊዮን ብር ያሻቀበው የመንግሥት የሀገር ውስጥ ብድር “ጫናው፣ ክምችቱ እየጨመረ፣ እየከፋ” ሊሔድ እንደሚችል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አብርሃም ዓለማየሁ አስጠንቅቀዋል። ሀገሪቱ በጦርነት የወደመውን መልሶ ለመገንባት የጀመረችው ጥረትም በታቀደው ፍጥነት ተግባራዊ አልሆነም።

https://p.dw.com/p/4gPxQ
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

Äthiopien | Flughafen in Addis Abeba
ምስል Eshete Bekele/DWምስል Eshete Bekele/DW

ከኤኮኖሚው ዓለም

በሣምንታዊው የከኤኮኖሚው ዓለም መሰናዶ የኢትዮጵያ፣ አፍሪካ እና ዓለምን ምጣኔ ሐብታዊ ይዞታ የተመለከቱ ትንታኔዎች፣ ቃለ መጠይቆች እና ዘገባዎች ይቀርባሉ። ይኸ መሰናዶ ሀገራት የሚያወጧቸውን ኤኮኖሚያዊ ፖሊሲዎች፣ መሪዎች የሚወስዷቸውን ምጣኔ ሐብታዊ ውሳኔዎች በመፈተሽ ጥቅም እና ጉዳታቸውን ያቀርባል።