1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአንጋፋው ጋዜጠኛ ፍቅሩ ኪዳኔ የቀብር ስነስረዓት ተፈጸመ

ዓርብ፣ ጥቅምት 11 2015

ባለፈው ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አንጋፋው የስፖርት ጋዜጠኛ ፍቅሩ ኪዳኔ የቀብር ስነስረዓት ዛሬ ፓሪስ ውስጥ ወዳጅ ዘመድ እና በርካታ ኣድናቂዎቻቸው በተገኙበት ተፈጽሟል።

https://p.dw.com/p/4IUQU
 Funeral of the renowned sport journalist Fikru Kidane
ምስል Haimanot Tiruneh/DW

የአንጋፋው ጋዜጠና ፍቅሩ ኪዳኔ የቀብር ስነ ስረዓት ተፈጸመ

ባለፈው ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት አንጋፋው የስፖርት ጋዜጠኛ ፍቅሩ ኪዳኔ የቀብር ስነስረዓት ዛሬ ፓሪስ ውስጥ ወዳጅ ዘመድ እና በርካታ ኣድናቂዎቻቸው በተገኙበት ተፈጽሟል። በቀብር ስነስረዓቱ ላይ የሬዲዮ ጣቢያችን ዶይቼ ቬለ በቀድሞ ባልደረባው አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን የገለጸበት መልዕክት በስነስረዓቱ ላይ ተነቧል።አንጋፋው የስፖርት ጋዜጠኛ ፍቅሩ ኪዳኔ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

Fikiru Kidane, Journalist, IOC-Funktionär und Schriftsteller
አንጋፋው ጋዜጠኛ ፍቅሩ ኪዳኔ ምስል Haimanot Tiruneh/DW

በስነ ስረዓቱ ላይ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ  አምባሳደርን ጨምሮ የበርካታ የአንጋፋ ኢትዮጵያውያን እና አለማቀፍ የስፖርት ሰዎች በአካል እና በቪዲዮ የተደገፈ የሀዘን መግለጫ ተላልፏል።

ኃይማኖት ጥሩነህ 

ታምራት ዲንሳ 

ኂሩት መለሰ