1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአረና ፓርቲ አቤቱታ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 23 2012

በትግራይ ክልል በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው የፖለቲካ ድርጅት ዓረና ትግራይ ለሉኣላዊነትና ዴሞክራሲ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች አባላቶቹ ላይ እስርና እንግልት እየደረሰ ነው ሲል አመለከተ። የአስተዳደር አካላት በበኩላቸው የፓርቲውን ክስ አይቀበሉትም።

https://p.dw.com/p/3Vbx7
Zusammenarbeit von Arena Tigray & Tigray democratic cooperation
ምስል DW/M. Haileselassie

«ፓርቲው አባላቴ ላይ ወከባ ተፈፅሟል ይላል»

በትግራይ ክልል በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው የፖለቲካ ድርጅት ዓረና ትግራይ ለሉኣላዊነትና ዴሞክራሲ  በተለያዩ  የክልሉ አካባቢዎች  አባላቶቹ  ላይ  እስርና  እንግልት  እየደረሰ  ነው  ሲል  ገለፀ።  የዓረና ትግራይ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዓምዶም ገብረ ሥላሴ ሰሞኑን በዓረና አባላት ላይ እየደረሰ ነው ያሉትን እስርና እንግልት በፓርቲው የምርጫ እንቅስቃሴ ላይ ጫና ለመፍጠር ያለመ ነው ብለውታል። የአስተዳደር  አካላት  በበኩላቸው  የፓርቲውን  ክስ  አይቀበሉትም። ከመቀሌ ሚሊየን ኃይለ ሥላሴ ከሁለቱም ወገን ያገኘውን እንደሚከተለው አጠናቅሮ ልኮልናል።

ሚሊየን ኃይለ ሥላሴ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ