Hirut Melesseረቡዕ፣ ሰኔ 19 2016የረቡዕ ሰኔ 16 2016 ዓ.ም.ቀን የዜና መጽሔት
በአማራ ክልል ከሚገኙ ትምሕርት ቤቶች ሦስት ሺው በክልሉ አለመረጋጋት ሲዘጉ ቁጥራቸው 3 ሚሊዮን የሚጠጋ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርታቸውን ማቋረጣቸውን የትምሕርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የሚገኙት የዘይሴ ብሔረሰብ አባላት በማንነታችን ምክንያት ወከባና እሥራት እየደረሰብን ነው ሲሉ ለዶቼቬለ ተናገረዋል። ከጎንደር ወደ መተማ የሚጓዙ ሾፌሮች በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ዒላማ ሆነናል ሲሉ አማረሩ። እነዚህ በዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅት ከተካተቱት ዘገባዎች መካከል ናቸው።