Eshete Bekeleእሑድ፣ ሐምሌ 7 2016በዶናልድ ትራምፕ ላይ ተኩስ የከፈተው ተጠርጣሪ ተሽከርካሪ ውስጥ ፈንጂዎች መገኘታቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ። ከግድያ ሙከራ ያመለጡት ትራምፕ አሜሪካውያን በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ ሲያቀርቡ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን በተፎካካሪያቸው ላይ የተሞከረውን ግድያ አውግዘዋል። እስራኤል በማዕከላዊ ጋዛ በሚገኝ ትምህርት ቤት ላይ ዛሬ እሁድ በፈጸመችው ጥቃት በርካታ ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር ባለሥልጣናት አስታወቁ። በጀርመን ባደን ቩተንበርግ ግዛት በምትገኘው ላውትሊንገን ከተማ አንድ ግለሰብ ሁለት ሰዎች ገድሎ ራሱን አጠፋ።