1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሐምሌ 13 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ሐምሌ 13 2016

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እንደ አዲስ ፓርቲ ለመመዝገብ ጥያቄ እንዳላቀረበ ቃል አቀባዩ አቶ አማኑኤል አሰፋ ተናገሩ። በአማራ ክልል የሚገኙ ሱዳናውያን ስደተኞችን ወደ ሌላ መጠለያ በማዘዋወር አውላላ እና ኩመር ጣቢያዎች በሒደት ሊዘጉ ነው። የኬንያ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ የመንግሥታቸውን ካቢኔ አስራ አንድ አባላት ይፋ አደረጉ። ናይጄሪያ “በርካታ እና ተደጋጋሚ ጥፋቶች” ፈጽሟል ያለችውን የፌስቡክ እና የዋትስአፕ ባለቤት ሜታ ኩባንያ 220 ሚሊዮን ዶላር ቀጣች። የእስራኤል ኃይሎች ዛሬ ቅዳሜ በጋዛ ሠርጥ የተለያዩ አካባቢዎች በፈጸሟቸው ድብደባዎች ቢያንስ 30 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የጤና ባለሥልጣናት አስታወቁ።

https://p.dw.com/p/4iXfW
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።