1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ቴክኒክአፍሪቃ

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: የፈጠራ ስራ ያቀረበች ብቸኛ ሴት

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 12 2014

በሀዋሳ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወጣት ቃል ኪዳን ደሳለኝ የ19 ዓመት ወጣትና የ12ኛ ክፍል ተማሪ ናት ፡፡ ተማሪ ቃል ኪዳን ሰሞኑን በሀዋሳ ከተማ በተካሄደው የሳይንስና ቴክኖሎጂ አውደ ርዕይ (ኤግዚቢሽን) ላይ ከትምህርት ቤት ጓደኞቿ ጋር በመሆን ለእይታ ያቀረበቻቸው የፈጠራ ሥራዎች አድናቆትን አስገኝተውላታል፡፡

https://p.dw.com/p/4A82i

ቃል ኪዳን ለዕይታ ካቀረበቻቸው የፈጠራ ስራዎች መካከል የህንፃ ዲዛይን እና ንብረት በሌባ ሲሰረቅ የደውል ጥሪ የሚያሰማ የፈጠራ ስራ ይገኙበታል። ወጣቷ ትምህርት ቤቷን ወክላ አውደ ርዕይ ያቀረበች ብቸኛ ሴት ተማሪ ናት። 

ዘገባ ፡ ሊሻን ዳኜ
ካሜራ ፡ ሸዋንግዛው ወጋየሁ