1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
እግር ኳስአፍሪቃ

ናይጀርያ ድል አልቀናዉም፤ እንግሊዝ ሩብ ፍፃሜ ደርሷል

ሰኞ፣ ነሐሴ 1 2015

የሴቶች የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ እንግሊዝ በአስደናቂ የፍፁም ቅጣት ምት በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍፃሜ አለፈች። ናይጀርያ ከብሪታንያ ጋር ዛሬ ባካሄዱት ግጥምያ ናይጀርያ በፍፁም ቅጣት ምት 4 – 2 ተሽንፋ ነዉ ከግጥምያዉ የወጣችዉ።

https://p.dw.com/p/4UsDp
WWCup Nigeria vs England
ምስል Tertius Pickard/AP/picture alliance

የሴቶች የዓለም  የእግር ኳስ  ዋንጫ እንግሊዝ በአስደናቂ የፍፁም ቅጣት ምት በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍፃሜ አለፈች። ናይጀርያ ከብሪታንያ ጋር ዛሬ ባካሄዱት ግጥምያ ናይጀርያ በፍፁም ቅጣት ምት 4 – 2 ተሽንፋ ነዉ ከግጥምያዉ የወጣችዉ። ይሁንና በእንግሊዝ የተሸነፉት የናይጀርያዉ ቡድን ዋና ስራ አስኪያጅ ራንዲ ዋልድሩም፤ የአውሮጳ ሻምፒዮን እንግሊዛዊ ድል ለናይጄሪያ የሴቶች እግር ኳስ እድገት ትልቅ አንድምታ እንዳለዉ ተናግረዋል። ስለዚህም ያለምንም ጭንቅላት መድፋት ቡድናቸዉ ቀና ብሎ ስና ሽንፈቱን ተቀብሎ ሻንጣዉን እንደሚሸክፉ ተናግረዋል። እንግሊዝ አሁን በመጪው ቅዳሜ ከኮሎምቢያ ወይም ከጃማይካ ወይ ጋር ትገናኛለች።

አዜብ ታደሰ

እሸቴ በቀለ