ሶማልያ፡ የኢጋድ ምክክርና በሰሜን ሶማሊያ የተጣሉ ጥቃቶች
ረቡዕ፣ ጥቅምት 19 2001ማስታወቂያ
በዚሁ የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን ኢጋድ በጠራው ጉባዔ ላይ የሶማልያ ጊዚያዊ ሁኔታ በዋነኝነት ተመክሮበታል። በዚሁ ጊዜ ዛሬ በሶማሊላንድ ርዕሰ ከተማ ሀርጌሳና በወደብ ከተማ ቦሳሶ በአንድ ጊዜ አካባቢ በተጣሉ አምስት የቦምብ ጥቃቶች በርካቶች መሞታቸውና ብዙዎች መቁሰላቸው ተሰምቶዋል። ለጥቃቱ እስካሁን ሀላፊነቱን የወሰደ ወገን የለም።