1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

DW Amharic የሰኔ 2 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleእሑድ፣ ሰኔ 2 2016

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጉዳት የደረሰበት በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ የሚገኘው አጼ ዮሐንስ አራተኛ ኤርፖርት ሥራ ጀመረ። በሶማሊያ ጋልጋዱድ ግዛት በተፎካካሪ ጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ቢያንስ 45 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 60 መቁሰላቸውን ባለሥልጣን ተናገሩ። እስራኤል አራት ታጋቾች ባስለቀቀችበት እና በስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ባካሔደችው ወታደራዊ ዘመቻ የተገደሉ ፍልስጤማውን ቁጥር ወደ 274 ማሻቀቡን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። አውሮፓውያን በአኅጉራዊው ምክር ቤት የሚወክሏቸውን ሕግ አውጪዎች ለመምረጥ ድምጽ ሲሰጡ ዋሉ። የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለሦስተኛ ተከታታይ የሥልጣን ዘመን ቃለ-መሐላ ፈጸሙ።

https://p.dw.com/p/4gqQT
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።