1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

DW Amharic የሚያዝያ 05 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ሚያዝያ 5 2016

ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ የባሕር ኃይል እንድታቋቁም እንደማትፈቅድ ሶማሊያ አስታወቀች። በውይይት ኢትዮጵያ ለንግድ አገልግሎት ወደብ የምታገኝበትን ዕድል ሶማሊያ ልታጤን እንደምትችል የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናግረዋል። የአፍሪካ ኅብረት ማሊ ወደ ሲቪል አስተዳደር የምትመለስበትን ፍኖተ-ካርታ እንድታቀርብ ጠየቀ። ናይጄሪያ አዲስ የማጅራት ገትር መከላከያ ክትባት ለዜጎቿ መስጠት ጀመረች። ጀርመን የሩሲያን ጥቃት ለመመከት ለዩክሬን ተጨማሪ ፓትሪዮት የአየር መከላከያ ሥርዓት ልትሰጥ ነው። የኢራን አብዮታዊ ዘብ አባላት ከእስራኤል ግንኙነት አለው የተባለ መርከብ ተቆጣጠሩ። በአውስትራሊያ በስለት በተፈጸመ ጥቃት ስድስት ሰዎች ተገደሉ።

https://p.dw.com/p/4ejDS
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።