ፓሪስ፤ የሽብር ሰለባዎችን አሰበች
እሑድ፣ ጥር 1 2008ማስታወቂያ
በፕሬዝዳንት ፍራንሷ ኦሎንድ እና የፓሪስ ከተማ ከንቲባ አኔ ሒዳልጎ ይፋ በተደረገው ቋሚ መታሰቢያ «በዚህ ቦታ የፈረንሳይ ዜጎች በጥር እና ኅዳር የሽብር ሰለባ ለሆኑት ያላቸውን ክብር ይገልጣሉ» የሚል ጽሁፍ ሰፍሯል። ፕሬዝዳንቱም ይሁኑ የፓሪስ ከተማ ከንቲባ ግን በስፍራዉ አንድም ቃል አልተናገሩም። ከመታሰቢያ ስነ-ስርዓቱ መጠናቀቅ በኋላ በቴሌቭዥን ንግግር ያደረጉት ከንቲባዋ ግን «ፓሪስ ፈርታለች። ይሁንና አሁንም በጽናት ቆመናል።» ሲሉ ባለፈው የጎርጎሪዮሳዊ አመት የተፈጸሙ የሽብር ጥቃቶች በከተማዋ ላይ ያሳደሩትን ጫና አስታውሰዋል።
እሸቴ በቀለ
ሸዋዬ ለገሠ