ግጭትና መፍትሄው ድራማ ክፍል 5
ረቡዕ፣ ጥቅምት 7 2005ማስታወቂያ
ይህ “እንዳባቶቻችን” የተሰኘው ተከታታይ የሬዲዮ ድራማ ክፍል አምስት ዝግጅታችን ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት ዝግጅታችን የኪጃኒ ሸለቆ ነዋሪዎች ወንዙ ጋር ተሰባስበው ነበር፡፡ እዚያም የቶሩቤና የኮሮማ ታጋዮች በማሳምቦና በሚቱምባ ተመርተው ወደ ጦርነት ሊገቡ ጥቂት ነበር የቀራቸው፡፡ ይሁንና ግን የእማማ ዋሊያኒ የእርቀ-ሠላም ሀሳብ አስፈሪውን ደም አፋሳሽ ግጭት ያስቀረው ይሆን? የዛሬውን “የአሸናፊነት ክፍያ” የተሰኘ ክፍል በማድመጥ መልሱን ያግኙ፡፡ ከዚያ በፊት ግን በመቶ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ በተዘጋ ቤት ውስጥ ወደተያዘው ስብሰባ እንውሰዳችሁ፡፡ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ማቶንጌን ጨምሮ ሁለት ታማኝ አማካሪዎቻቸው ማለትም የጦር ሀይሉ ጄነራል ሶምባና የደህንነቱ ሃላፊ ኬሮ ናቸው ስብሰባውን የያዙት፡፡