ጀርመን የምርጫ ዘመቻ
ማክሰኞ፣ መስከረም 2 2010ማስታወቂያ
ጀርመን ዉስጥ ከ12ት ቀናት በኋላ በሚደረገዉ አጠቃላይ ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ዕጩዎቻቸዉ በየአካባቢዉ የሚያደርጉት የምርጡኝ ዘመቻና ቅስቀሳ ሰሞኑን እየተጠናከረ ነዉ።ዘንድሮ በሚደረገዉ ምርጫ አማራጭ ለጀርመን (AFD-በጀርመንኛ ምሕፃሩ)ን የመሳሰሉ ቀኝ አክራሪ ፓርቲዎች ሥለሚወዳደሩ የምርጫ ዘመቻ ፉክክሩ ከዚሕ ቀደም ከሚታወቀዉ ጠንከር ያለ ነዉ።ዶቸ ቬለ በተለይ ቀኝ ፅንፈኞች በብዛት ይጉኙበታል በሚባለዉ አካባቢ የሚደረገዉን የምርጫ ዘመቻ የሚከታተል የጋዜጠኞች ቡድን አሰማርቷል።ባልደረባችን ማንተጋፍቶት ሥለሺ የቡድኑ አባል ነዉ።በስልክ አነጋግሬዉ ነበር።
ማንተጋፍቶት ሥለሺ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ