ደመወዝ ጭማሪ፤ የኑሮ ውድነትና የኤኮኖሚ ይዞታ
እሑድ፣ ነሐሴ 11 2006ማስታወቂያ
አቅም አላት» ሲል የዓለም ባንክ የተናገረላት ኢትዮጵያ፣ ከ 2003 ዓ ም ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ቁጥራቸው ከ 1,3 ሚሊዮን ለማያንሱት የመንግሥት ሠራተኞች ፣ የደመወዝ ጭማሪ እንደሚደረግ ጠ/ሚንስትሩ ባለፈው ሰኔ 16 ,2006 ዓ ም፣ ይፋ ካደረጉና ዘግየት ብሎም በገንዘብና የኤኮኖሚ ልማት ሚንስቴር፣ እንዲሁም የሲቭል አገልግሎት መሥሪያ ቤት ጭማሪው ከ33%-46% እንደሚዘልቅ ካሳወቁ ወዲህ፣ ጉዳዩ ዐቢይ የመነጋገሪያ ርእስ ሆኖ መቀጠሉ የታወቀ ነው።
ከጭማሪው ሠናይ ዜና ጋር ተያይዞ የዋጋ መናር መቅኖ ያሳጣዋል ከሚለው ሥጋት ጋር ፤ ለደመወዝ ማስተካከያው፣ በዓመታዊው በጀት ላይ 10,3 ቢሊዮን ብር ይጨመራል መባሉ፣ የገንዘብና የኤኮኖሚ ጠበብት የተለያዩ ሐሳቦችን እንዲያንጸባርቁ መጋበዙም አልቀረም።
ስለ ደመወዝ ማስተካከያውና የሀገሪቱ የኤኮኖሚ አቅም፣ ባለሙያዎች ምን ይላሉ? ዶቸ ቨለ ለዚህ ሳምንት የመረጠው የውይይት ርእስ ነው።
ተክሌ የኋላ
አዜብ ታደሰ