1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ጉዳይ

ረቡዕ፣ መስከረም 28 2012

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 20/80 በሚለው የገንዘብ ቁጠባ ስልት ገንዘብ ላጠራቀሙ ወገኖች የገነባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እደላ ጉዳይ ዛሬም ማነጋገሩ አላበቃም።

https://p.dw.com/p/3QzB0
Baustelle in Addis Abeba Äthiopien
ምስል Getty Images/AFP/Z. Abubeker

የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች

 ከሰሞኑ አስተዳደሩ በልማት ሰበብ ከመሬታቸው ለተነቀሉ ወገኖች ቤቶቹን በዕጣ ሊሰጥ ነው መባሉን መነሻ በማድረግ ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር በልማት ምክንያት ይነሱ የነበሩና በአዲስ አበባ ከተማ ዳርቻዎች ይኖሩ የነበሩ አርሶ አደሮች በ20 / 80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መርሃ ግብር ግንባታ ውስጥ ምትክ ቤት እንዲሰጣቸው የተወሰነው ታህሳስ 24 ቀን  2011 ዓ.ም መሆኑን አመልክተዋል።  ይህም በከተማው ካቢኔ ውሳኔ ግንቦት 2011 ዓ.ም ተግባራዊ መደረጉን በመጥቀስ  እንደ አዲስ የሚያወዛግብ ነገር አይደለም ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ኢንጂኒየር ደሳለኝ ተረፈ ተናግረዋል። ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝሩን ልኮልናል።

ሰሎሞን ሙጬ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ