የፖለቲካ ፓርቲዎችና አዲሱ ዓመት
ሰኞ፣ መስከረም 3 2008ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ፊደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ «መድረክ» በአጭሩ ፤ የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ « ኢራፓ» ሰማያዊ ፓርቲ፤ አንድነትና የመላዉ የኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት «መኢአድ» አመራር አባላት ለዶቼ ቬለ በአዲሱ ዓመት ሰላማዊዉን የሕዝብ ንቅናቄ አጠናክረዉ እንደሚቀጥሉበት ተናግረዋል። ያለፈዉ ቁርሾ በብሔራዊ ዕርቅና መግባባት እንዲፈታ የትግል አቅጣጫዬ አድርጌ እንቀሳቀሳለሁ ሲል የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ «ኢራፓ » ገልፆአል። የሰማያዊ ፓርቲ ለቀመንበር በበኩላቸዉ ፓርቲያቸዉ በቅርቡ ጉባኤ ማካሄዱንና የካቢኔ አባላት የመሰየም ሂደት በቅርቡ እንደሚካሄድ ገልፀዋል።
ዮኃንስ ገብረግዚአብሄር
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ