የጀርመን የልማት ተራድኦ
ዓርብ፣ መጋቢት 10 2002ማስታወቂያ
የጀርመን መንግስት የልማት ዕርዳታ ተግባራትን በዋነኛነት የሚያከናውነው በ 3 መስሪያ ቤቶች አማካይነት ነው ። እነርሱም በእንግሊዘኛው ምህፃር GTZ በመባል የሚጠራው የጀርመን የቴክኒክ ተራድኦ ድርጅት፣ በምህፃሩ DED የተሰኘው የጀርመን የልማት ዕርዳታ ድርጅት እንዲሁም KfW በሚል ምህፃር የሚታወቀው የጀርመን የመልሶ ግንባታ አባዳሪ ባንክ ናቸው ። የጀርመን መንግስት የዕርዳታ ድርጅቶች በአንድ ማዕከል እንዲዋቀሩ ለማድረግ ካሰበ ቆየት ብሏል ። ወጪና ገቢን የሚቆጣጥረው የፌደራሉ መንግስት መስሪያ ቤት እንደሚለው 1400 የሚሆኑ ሰራተኞች በ 3ቱ መስሪያ ቤቶች ውስጥ አላስፈላጊና ተደጋጋሚ በሆነ መዋቅር ነው የሚሰሩት።
ዳንኤል ሼሽከቪች፤ ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ