የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ድልና የሽቫይንሽታይገር ስንብት
ሐሙስ፣ ነሐሴ 26 2008ማስታወቂያ
ብሔራዊ ቡድኑ ትናንት ምሽት በጀርመን የመንሽንግላድባህ ከተማ ከፊላንድ ጋር ባደረገዉ የወዳጅነት ግጥምያ 2 ለ 0 በሆነ ዉጤት አሸንፎአል። የስንብት ግጥምያ የተደረገለትና ትናንት በቡድኑ ለመጨረሻ በአንበልነት በመምራት የተጫወተዉ ሽቫይንሽታይገር፤ በብሔራዊ ቡድኑን ወክሎ ሲጫወት የትናንትናዉ 121ኛ ጊዜ መሆኑም ታዉቋል። ባስቲ ሲሉ የሚጠሩትን የተወዳጁን የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አንበል በቡድኑ የመጨረሻ ግጥምያን በሞንሽንግላድባህ በሚገኘዉ ስቲዲዮም ለመከታተል የገባዉ ሰዉ 30 ሺህ እንደሆነም ተመልክቶአል። ሽቫይንሽታይገር በማንችስተር ቡድን ተሰልፎ እንደሚጫወት ይታወቃል።
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ