የወዳጅነት ትምሕርት ቤት
ዓርብ፣ ጥቅምት 27 2002ማስታወቂያ
የበርሊን ግንብ ከመናዱ በፊት የጀርመን ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ (የምሥራቅ ጀርመን) ፖለቲከኞች ሕልም-አለማ ብዙ፥ ሩቅም አይነት ነበር።ምሥራቅ በርሊኖች እንደ ሞስኮና ሐቫና ብጤዎቻቸዉ ሁሉ ከሚንስታዊዉን ርዕዮተ-አለም በመላዉ አለም ለማስረፅ በየሐገሩ በተለይም ምጣኔ ሐብታዊ ችግር በተጫጫናቸዉ፣ የምዕራቡ ፖለቲካዊ ስርዓት ባማረራቸዉ አፍሪቃን በመሳሰሉት ሐገራት ወጣቶች ልዩ ላይ ትኩረት አድርገዉ ነበር።
በየሥፍራዉ በጣሙን በአፍሪቃ ዉስጥም አባባሪ-ተባባሪ አላጡም።ከአፍሪቃ አንዱ የሞዛምቢክ የመጀመሪያ መሪ ሳሞራ ማሼል አንዱ ነበሩ።የዶቼ ቬለዋ ባልደረባ ማርታ ደ አልማይዳ ባሮሶ እንደ ዘገበችዉ የማሼል-ሆኔክር የሩቅ እቅድ ወጣቶችን በኮሚንዝም ርዕዮት አንፆ ሥርዓቱን የዝንተ-አለም፥ የመላዉ አለም ርዕዮት የማድረግ አይነት ነበር።ባንድ የቀድሞ ትምሕር ቤት ላይ የተመሠረተዉን የባሮሶን ዘገባ ይልማ ሐይለ-ሚካኤል አጠናቅሮታል።
ማርታ ባሮሶ/ ይልማ ሐይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ