በኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ረቂቅ ላይ የተሰዙ አስተያየቶች
ማክሰኞ፣ ሰኔ 27 2009ማስታወቂያ
ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ያላትን ልዩ ጥቅም አስመልክቶ የኢትዮጵያ የሚንስትሮች ምክር ቤት ያፀደቀዉን አዋጅ የኦሮሞ ዲሞክራስያዊ ግንባር ተቃወመ። የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ሊንጮ ለታ እንደገለፁት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በሌላ መልኩ ሥራ ላይ ለማዋል እና ማኅበረሰቡን ለማጋጨት የታለመ ሊሆን ይችላል። የአፍሪቃ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጋሩማ በቀለ ጋሩሳ በበኩላቸዉ የመግለጫዉ ጽንሰ ኃሳብ ኦሮሞዎች በአዲስ አበባ ላይ ያላቸዉን ጥቅም የሚያነፀባርቅ ሆኖ እንዳላገኙት ነዉ የገለፁት ። አቶ ሌንጮ ለታንና አቶ ጋሩማ በቀለን ያነጋገረዉ የዋሽንግተኑ ወኪላችን ዝርዝር ዘገባዉን ልኮልናል።
መክብብ ሸዋ
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለስ