የኢድ አልፊጢር በአል በአዲስ አበባ
ሰኞ፣ መስከረም 3 2003ማስታወቂያ
ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ደግሞ በአሉን በዘመን መለወጫ በአል-ዝግጅት ጭምር ነዉ-ያከበሩት።ከአዲስ አበባ እንጀምር። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ታደሠ እንግዳዉ የርዕሠ-ከተማይቱ የበአል-አከባበር ተከታትሎት ነበር።
መቀሌ-ትግራይ፤ ወኪላችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር እንደተመለከተዉ በአሉ በተለይ ጎደና ሰማዕታት ተብሎ በተሰየመዉ አዲስ አዉራ ጎዳና ላይ በተደረገ የአል-መሻድ ስገት ነበር የተጀመረዉ።
የአስመራዉ ወኪላችን ጎይቶም ቢሆን እንደተከታተለዉ የኤርትራ በተለይ ደግሞ የአስመራ አዉራ መንገዶች በበዓለተኛዉ ተጨናንቀዉ ነዉ-ነበር ያረፈዱት።
ቀይ ባሕር ማዶ ሳዑዲ አረቢያ በተለይም በሙስሊሞቹ ቅዱስ ስፍራዎች መካሕ እና መዲና ዉስጥ በተደረገዉ የአል-መሻድ ስግደት ከ2.5 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ተካፍሏል። የጂዳዉ ወኪላችን ነብዩ ሲራክ እንደታዘበዉ ሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ኢድ አልፊጥርን ያዉ እንደበአል በደስታ ቢያከብሩም-የበአል ደስታቸዉ በታሰሩ ወገን-ዘመዶቻቸዉ ስቃይ እሁለት የተከፈለ ነበር።
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ