የኢትዮ-ሱዳን ና ግብፅ ዉዝግብ
ረቡዕ፣ መጋቢት 29 2013ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ በምታስገነበዉ የሕዳሴ ግድብ ሰበብ ከሱዳንና ግብፅ ጋር የገጠመችዉ ዉዝግብ እየተካረረ ነዉ።ዉዝግቡን በድርድር ለመፍታት የሶስቱ ሐገራት ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ትናንት ኪንሻ-ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ዉስጥ አድርገዉት የነበረዉ ስብሰባ ያለዉጤት አብቅቷል።ስብሰባዉ ከተበተነ በኋላ የሱዳን ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ኢትዮጵያ የምትወስደዉ ርምጃ የዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ ነዉ በማለት ወቅሰዋል።የኢትዮጵያ የዉኃ ሚንስትር ስለሺ በቀለ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሱዳን የድርድሩን ሒደት ለመቀየር ሞክራ ነበር በማለት ካርቱም ወቅሰዋል።ከሕዳሴ ግድብ በተጨማሪ ሱዳን ከደቡብ ሱዳን ጋር በምትወዛገብበት አብዬ ግዛት የሰፈረዉ የኢትዮጵያ ሠላም አስከባሪ ሠራዊት እንዲወጣ ጠይቃለችም።
ሰለሞን ሙጬ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ