የኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ተቃዉሞ በለንደን
ዓርብ፣ ነሐሴ 24 2005ማስታወቂያ
ተሰላፊዎቹ ሰላማዊ ትግሉ ይቀጥላል፤ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሙስሊሞች መብት ይከበር፤ ኢትዮጵያ የሁሉም ሃይማኖት ሀገር ናት የሚሉ መፈክሮች ሲያሰሙ እንደነበር ተገልጿል። ሰልፉ የተካሄደዉ በእንግሊዝ የፓርላማ አደባባይ ከፓርላማዉ ፊት ለፊት ሲሆን በስፍራዉ ተገኝታ ሁኔታዉን በተከታተለችዉ ዘጋቢያችን ሃና ደምሴ ግምት ከሁለት መቶ በላይ ሰልፈኞች ተገኝተዋል። ወደሎንዶን ደዉዬ ሰልፉ በሚካሄድበት ሰዓት እዚያ የተገኘችዉን ሃናን እና ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱን ስለሁኔታዉ አነጋግሬያለሁ፤
ሃና ደምሴ
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ