የኢትዮጵያና የሱዳን ዉዝግብ፤ ቃለ መጠይቅ
ሰኞ፣ ጥር 24 2013ማስታወቂያ
የካርቱምና የአዲስ አበባ ገዢዎች ሲወዳጁ ሕዝባቸዉን ወድማማች እሕትማማች እያሰኙ ያስጨፍሩ-ያዘምሩታል።ዐኽዋን ዐኽዋን ኢትዮጵያ ወ ሱዳን እንደሚባለዉ።» ሲጋጩ «ታሪካዊ» ጠላትነታቸዉን እያስፈከሩ ሲያላትሙት ዘመናት አስቆጠሩ።ሐቻምና ይሔኔ የአዲስ አበባ መሪዎች ካርቱሞችን ሸምጋይ፣አስታራቂ፣ ለሱዳን ሕዝብ ችግር ደራሽ ነበሩ።ፍቅር፣ወዳጅነት፣ መደጋገፉ በሁለተኛ ዓመቱ ዘንድሮ በንንኖ ለዉጊያ የሚፈላለጉ ጠበኞች ሆኑ።የሁለቱን ሐገራት ዉዝግብ በተመለከተ የኢትዮጵያ የስልታዊ (ስትራቴጂያዊ) ጥናት ማዕከል ኃላፊና የሱዳን ጉዳይ የፖለቲካ አጥኚ ዶክተር ሙባረክ ሚፍታሕ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገናል።በቃለ መጠይቁ የሱዳኖች አላማ፣ የግብፅ ሚና ወይም ጫና፣ የኢትዮ-ሱዳን ታሪካዊ ግንኙነት፣ የጠቡ መነሻ፣ ምክንያቱና መፍትሔዉ ተነስቷል። ሙሉ ቃለ መጠይቁን እነሆ-
ነጋሽ መሐመድ
ማንተጋፍቶት ስለሺ