የአፍሪቃ ጋዜጠኝነትና የIFJ ዘገባ14 ጥር 2002ዓርብ፣ ጥር 14 2002በአዉሮጳዉያኑ 2009ዓ,ም የአፍሪቃን የፕረስ ነጻነት ይዞታ ትናንት ይፋ ያደረገዉ የአፍሪቃ የጋዜጠኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዓመቱ ለአፍሪቃ ጋዜጠኞችና ለጋዜጠኝነት እጅግ አስቀያሚዉ እንደነበር አስታወቀ።https://p.dw.com/p/LeImማስታወቂያ በዓመቱ በአፍሪቃ ብቻ የሙያ ግዴታቸዉን በመወጣት ላይ እንዳሉ 13 ጋዜጠኞች መሞታቸዉን ፌዴሬሽኑ አመልክቷል። 32ጋዜጠኞች ደግሞ በወህኒ ይማቅቃሉ፤ ቁጥራቸዉ የበዙት ጋዜጠኞች ተይዘዉ ይለቀቃሉ፤ አንዳንዶቹ በከፋ ሁኔታ ጥቃት ደርሶባቸዋል፤ ስጋትና ማዋከብም ለአፍሪቃ ጋዜጠኞች በዕለት ከዕለት ስራቸዉ ዋናዉ መሰናክል ሆኖ ቀጥሏል እንደድርጅቱ ዘገባ። ታደሰ እንግዳዉ ሸዋዬ ለገሠ ሂሩት መለሰ