የአፍሪቃ ካቶሊካዉያን ሲኖዶስ25 መስከረም 2002ሰኞ፣ መስከረም 25 2002ለሶስት ሳምንታት የሚዘልቀዉ የአፍሪቃ ክፍለ ዓለም የካቶሊካዉያን ጳጳሳት ሲኖዶስ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት 16ኛ ሊቀ መንበርነት ዛሬ ረፋዱ ላይ በቫቲካን ተጀምሯል።https://p.dw.com/p/JyKRጳጳሳቱ በቫቲካንምስል APማስታወቂያ ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደዉ ይህ የአፍሪቃ ካቶሊካዉያን ጳጳሳት ሲኖዶስ «የአፍሪቃ ቤተክርስቲያን በእርቅ፤ ፍትህና ሰላም አገልግሎት» በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሂድ ሲሆን በጉባኤዉ ጅማሬ ዋዜማ ትናንት ጠቅላላ የአፍሪቃ ጳጳሳትና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት የተመራ ስርዓተ ቅዳሴ ተከናዉኗል። ተኽለእግዚ ገ/ኢየሱስ/ሸዋዬ ለገሠ/ ተክሌ የኋላ