የአቡነ ጳዉሎስ ዜና ዕረፍት
ሐሙስ፣ ነሐሴ 10 2004ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳዉለስ ዛሬ ሲነጋጋ አርፈዋል።አቡነ ፓዉሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያንን ላለፉት ሃያ ዓመታት የመሩ መንፈሳዊ አባት ነበሩ።ያም ሆኖ አመራራቸዉ ተቃዉሞ አልተለየዉም ነበር።የርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳቱን ሞት በተመለከተ የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ የቤተ-ክርስቲያኒቱን ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ፥ አገልጋዮችንና ምዕመናንን አነጋግሮ ያጠናቀረዉ ዘገባ አለዉ።
አበበ እንደተከታተልከዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት አቡነ ጳዉሎስ አርፈዋል።እንደምናዉቀዉ እዚያ ዩናይትድ ስቴትስ የእሳቸዉን አመራር የሚቀበሉም የሚቃወሙም እንዲያዉም የተለየ ሲኖዶስ የሰየሙ የሐይኖት መሪዎች፥ ሁለቱን ወገኖች ለማደራደር የሞከሩ ወገኖችና በርካታ ምዕመናን አሉ ምን አሉ የአቡነ ጳዉሎስን ዜና ዕረፍት ሲሰሙ፣-
----------------------------------
ከዚሕ በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አመራር እንዴት መሆን አለበት ይላሉ፥ ድርድሩስ ይቀጥላል የሚል አስተያየት አለ?
ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ
አበበ ፈለቀ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ