የአሸባብ አመፅ በኬንያ
ማክሰኞ፣ መስከረም 14 2006ማስታወቂያ
በኬንያ የሚኖሩ የጎረቤት አገሮች ስደተኞችም ከጥቃቱ ጋ በተያያዘ ስጋት ገብቶናል እያሉ ነው። የፀጥታ ጥናት ተቋም በበኩሉ ለዚህ አይነቱ አደጋ ወታደራዊ ርምጃ ብቻውን መፍትሄ አይሆንም ባይ ነው።
አሸባብ ናይሮቢ በሚገኝ የገበያ አዳራሽ ላይ ባደረሰው ጥቃት የአሜሪካ ፖለቲከኞችን እያወዛገበ ነው።የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ መስተዳድር አደጋውን የጣሉትን ወገኖች ተከታትሎ ለመያዝ እና ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈፀም ለመከላከል ከኬንያ እና ከሌሎች የአካባቢው መንግስታት ጋ አብሮ እንደሚሰራ አስታውቋል። ባለሙያዎችም ወደ ኬንያ ተልከዋል። በሌላ በኩል የኦባማ መንግስት ተቃዋሚዎች ዮናይትድ ስቴትስ በአሸባብ ላይ ቀጥታ ወታደራዊ ርምጃ መውሰድ አለባት እያሉ ነው። ዝርዝር ዘገባዉን ከሶስት ዘገባዎች በድምፅ ያገኛሉ።
ጃፈር አሊ
ሀና ደምሴ
አበበ ፈለቀ
ነጋሽ መሐመድ