የንባብ ባህል በኢትዮጵያ
ዓርብ፣ ሐምሌ 29 2008ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ የንባብ ባህልን ለማዳበር አሁን አሁን በተበታተነ መልኩም ቢሆን ጥረቶች እየተደረጉ ነው ። በዚህ ረገድ ንባብ እና መጻህፍት ላይ ያተኮሩ አውደ ርዕዮች ይጠቀሳሉ ። ስለ ሀገር ልማት ሲታሰብ ከቁሳዊ ልማት ባሻገር ሰብዓዊ ልማት ዋናው ነው ። በዚህ ረገድ መጻህፍት እና ንባብ ትልቁን ሚና ይጫወታሉ። በሀገሪቱ የአንባቢ ቁጥር እና የንባብ ባህል ጥናት የሚያስፈልገዉ ቢሆንም ፤የመጻህፍት ዋጋ መናር እና የቤተመጻህፍት ቁጥር አነስተኛ መሆን በችግርነት ይጠቀሳሉ ።በመሆኑም ከግለሰብና ተቁማት የተበታተነ ጥረት በተጨማሪ ለንባብ ባህል መዳበር መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ ንባብን ትኩረት አድርገዉ የሚስሩ አካላት ትናግረዋል። የነዚህ ዐውደ ርዕዮች ፋይዳ ፣እንዲሁም የንባብ ባህልን ለማዳበር የሚደረጉ ጥረቶች እና ተግዳሮቶቹ የዛሬው የባህል መድረክ ትኩረት ነዉ።
ፀሐይ ጫኔ
ነጋሽ መሐመድ