የነአቶ እስክንድር ነጋ የፍርድ ቤት ዉሎ
ሰኞ፣ ጥቅምት 15 2014ማስታወቂያ
በማረሚያ ቤት ውስጥ እያሉ የድብደባ ወንጀል እንደተፈፀመባቸው ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፖርቲ ፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ አቤቱታቸው በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና እና በፌዴራል ወንጀል ምርመራ እንዲጣራ በፍርድ ቤት ታዘዘ።
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የፀረ ሽብር እና የሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዛሬው ዕለት ካለፈው ሳምንት ያደረውን የዐቃቤ ሕግን የ1ኛ ምስክር ድጋሜ ጥያቄ እና የፍርድ ቤት የማጣሪያ ጥያቄዎችን አድምጣል።
በመቀጠል የዐቃ ሕግ ሁለተኛ ምስክርነትን አድምጧል። ፍርድ ቤቱ ከአንደኛ ተከሳሽ ከቤተሰብ ጋር በስልክ ልገናኝ የሚልንና እና ከሁለተኛ ተከሳሽ ውጪ በግል ልታከም በሚል የቀረቡ የመብት ጥያቄዎችን ካደመጠ በኋላ ትዕዛዝ ለመስጠት ለጥቅምት 17 ቀን ቀጠሮ ሰጥቷል። የዐቃቤ ሕግ ምስክር የመሥማት ሂደት ደግሞ ነገ እንዲቀጥል ችሎቱ አዟል።
ሰለሞን ሙጬ
አዜብ ታደሰ
እሸቴ በቀለ