የታገተቱ ተማሪዎች የት ናቸዉ?
ሐሙስ፣ ጥር 7 2012ማስታወቂያ
ከደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ የትዉልድ አካባቢያቸዉ ሲጓዙ ማንነታቸዉ ባልታወቀ ሰዎች የታገቱት የአማራ ተማሪዎች መለቀቅ-አለመለቀቃቸዉ ዛሬም እያከራከረ ነዉ።ባለፈዉ ሕዳር 24 ከደንቢዶሎ ወደ ጋምቤላ ሲጓዙ የታገቱት ባብዛኛዉ ሴት ተማሪዎች መለቀቃቸዉን የኢትዮጵያ መንግሥት ባለስልጣናት አስታዉቀዉ ነበር።ከእገታዉ ያመለጠች አንዲት ተማሪ የጠቀሰችዉ የታጋቾች ቁጥር መንግስት የገለጠዉ ቁጥርም ይለያያል። የተማሪዎቹ ወላጆችና የአማራ መስተዳድር ተቃዋሚ ፖለተከኞች እንደሚሉት መንግሥት ሥለተማሪዎቹ መለቀቅ የሰጠዉ መግለጫ እዉነትነት እያጠራጠረ ነዉ።ተለቀቁ የተባሉት ተማሪዎች እስካሁን ከወላጅ፣ ዘመድ ወዳጅ ጋር አልተገናኙም።
ዓለምነዉ መኮንን
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ