1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የታኅሳስ 29 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleሰኞ፣ ታኅሣሥ 29 2016

የሶማሊያ ፕሬዝደንት ሐሰን ሼይክ ሞሐመድ ከኤርትራ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለመነጋገር አስመራ ገቡ። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ዛሬ ሰኞ ከሶማሌላንድ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ኑር ኢስማኤል ታኒ ጋር በአዲስ አበባ ተገናኝተዋል። በላይቤሪያ የነዳጅ ማጓጓዣ ቦቴ ሲፈነዳ የገደላቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 74 ማሻቀቡን የሀገሪቱ መንግሥት አስታወቀ። በኢራን የሚደገፈው የሒዝቦላህ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ በደቡባዊ ሊባኖስ በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ። የጀርመን መንግሥት በሒደት የግብርና ድጎማ ለማቋረጥ ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃወም ሰልፍ የወጡ ገበሬዎች በትራክተሮቻቸው መንገድ ዘጉ።

https://p.dw.com/p/4azU3
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።