የቦይንግ 737 አደጋ አንደኛ ዓመት
ማክሰኞ፣ መጋቢት 1 2012ማስታወቂያ
ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ተከስክሶ የ157 መንገደኞች እና የበረራ ሠራተኞች ሕይወት የተቀጠፈበት አደጋ ከደረሰ ዛሬ አንድ ዓመት ደፈነ። የአደጋውን ሰለባዎች የሚያዘክሩ የተለያዩ ዝግጅቶች ከትናንት በስተያ እሁድ ጀምሮ በተለያዩ ስፍራዎች እየተካሄዱ ነው። ዛሬም በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች ቤተሰቦች አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ስፍራ በመገኘት ሙት ዓመቱን አስበዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በበኩል በአብራሪዎች ክበብ ቅጥር ግቢ ውስጥ ማምሻውን የመታሰቢያ ሥርዓት እያካሄደ ነው። ዝግጅቱ ይጀመራል ከተባለው ሰዓት ዘግይቶ ሊጀመር አካባቢ በስፍራው የሚገኘውን ዘጋቢያችንን ሰሎሞን ሙጬን ስቱዲዮ ከመግባቴ በፊት አነጋግሬዋለሁ።
ሰሎሞን ሙጬን
ሸዋዬ ለገሠ
ማንተጋፍቶት ስለሺ