የቤንች ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ወቀሳ13 መጋቢት 2002ሰኞ፣ መጋቢት 13 2002በደቡብ ክልል የሚንቀሳቀሰው የተቃዋሚው ፓርቲ፡ የቤንች ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ለግንቦት 2002 ዓም በሚያካሂደው የምርጫ ዘመቻ ወቅት በአባሎቹና በደጋፊዎቹ ላይ ከገዢው ፓርቲ አባላት የኅል ተግባር እንደሚፈጸምበት የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ገዘኸኝ ባዲኮምስ ለዶይቸ ቬለ ገለጹ፥https://p.dw.com/p/MZO5ምስል APማስታወቂያድርጅታቸው ለአካባቢው የምርጫ ጽህፈት ቤት እና ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ስለዚሁ ጉዳይ አቤቱታ ቢያቀርብም መልስ እንዳላገኘም አቶ ገዘኸኝ አክለው አስረድተዋል። ይሁንና፡ የሚዛን ተፈሪ የምርጫ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚናስ ከበደ ይህንኑ የአቶ ገዘኸኝን አባባል በማስተባበል ጽህፈት ቤታቸው መልስ መስጠቱን ነው ያመለከቱት። አርያም ተክሌ ነጋሽ መሐመድ