የሲዳማ ብሄረሰብ ባህላዊ ገጽታ
ዓርብ፣ ሰኔ 4 2002ማስታወቂያ
በያዝነዉ አመት በተደረገ የጥናት መረጃ የሲዳማ ዞን 3.2 ሚሊዮን ህዝብ መያዙ ተነግሮአል። የለቱ የባህል ጥንቅራችን የሲዳማ ብሄረሰብ ባህላዊ ገጽታዎችን ይቃኛል።
በደቡብ ኢትዮጽያ በይርጋለም ከተማ ነዋሪ የሆነዉ ጋዜጠኛ ቦጋለ ጥላሁን የረጅም ግዜ አድማጫችን ብቻ ሳይሆን ተሳታፊም ነዉ። በኢትዮጽያ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችን አቅፎ በሚገኘዉ በደቡብ ዞን አጓጓጊ የሆኑ የተፈጥሮ መስቦችን አሉት የሚለን ጋዜጠኛ ቦጋለ ከአዲስ አበባ 320 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘዉ በይርጋለም ከተማ ነዋሪ ሲሆን ስለ ሲዳማ ብሄረሰብ ባህል በተለይም ሆሪ ተብሎ ስለሚታወቀዉ ያላገቡ የሲዳማ ልጃገረዶች የዘፈን ዉዝዋዜ፤ ስለ ቋንቋዉ፣ ስለ ሰርግ፣ እንዲሁም ሌሎች የባህል ገጽታዎች ያጫዉተናል። በሌላ በኩል በሲዳማ ዞን ባህልና እስፖርት ማዕከል ድምጻዊ የሆነችዉ ትብለጽ ተከስተ በሲዳማ ቋንቋ በምታዜመዉ ዘመናዊ ሙዚቃዋ በአካባቢዉ ተወዳጅነትን ማትረፍዋ ነገርላታል። የሲዳማ ዞን የተፈጥሮ መስቦች ያሉበት በቱሪስቶች የሚወደድ ድንቅ የተፈጥሮ ጸጋ ያለዉም አካባቢ ነዉ መረሃ ግብሩን ያድምጡ
አዜብ ታደሰ፣ ነጋሽ መሃመድ