"የሰው አካል የሚመስል ምንም ማግኘት አይቻልም" ዶክተር ሰለሞን አሊ
ሰኞ፣ መጋቢት 2 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር፤ የቻይና እና የእስራኤል ባለሙያዎች ከትናንት ጀምሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ 302 ቦይንግ 737 -800 ማክስ አውሮፕላን ከተከሰከሰበት ቦታ ፍለጋ ሲያካሒዱ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የሰብዓዊ ዲፕሎማሲ፤ የገቨርናስና የዓባላት ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ሰለሞን አሊ "የሰው አካል ነው ብለህ የምትላቸው ነገሮች የሉም። ሕይወት ለማዳን የሚቻልበት አይነት ኹኔታ አልነበረም። ስለዚህ እዚያ አካባቢ ተበታትነው የነበሩ ቁሳቁሶችን፤ ንብረቶችን፤ አንዳንድ የሰውነት ክፍሎችን" በጎ ፈቃደኞች ከትናንት ጀምሮ መሰብሰባቸውን ለDW አስረድተዋል።
ዶክተር ሰለሞን "የሰው አካል የሚመስል ምንም ማግኘት አይቻልም። ከደረሰን ሪፖርት እና ከፎቶግራፎች እንዳየንው ብጥቅጣቂው ራሱ በጣም ትንንሽ ነው" ሲሉ አክለዋል። በጎ ፈቃደኞች በቦታው ከነሩ የጸጥታ አስከባሪዎች፤ የሕክምና ባለሙያዎች እና ከሌሎች አገራት ከተጓዙ ባለሙያዎች አጠገብ ሆነው የተቀዳደዱ መፃሕፍት፤ መታወቂያዎች፤ ፓስፖርቶች ሰብስበዋል።
ሙሉ ቃለ መጠይቁን የድምፅ ማዕቀፉን በመጫን ያድምጡ
እሸቴ በቀለ
ተስፋለም ወልደየስ