አንድ መቶ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታሰሩ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 4 2008ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግስት የፀጥታ ሐይላት ሰሞኑን አንድ መቶ ያሕል ባለሥልጣናትና አባላቱን ማሰራቸዉን ተቃዋሚዉ የሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ አስታወቀ።የፓርቲዉ ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ለገሰ ተፈረደኝ እንዳሚሉት ባለሥልጣናቱና አባላቱ የታሠሩት አማራ፤ ኦሮሚያ እና አዲስ አበባ መስተዳድር ዉስጥ ነዉ።ከታሠሩት መካከል አዲስ አበባ የሚገኙት ብቻ ፍርድ ቤት ሲቀርቡ የተቀሩት እስካሁን ፍርድ ቤት አልቀረቡም።አንዳዶቹም ያሉበት ሥፍራ አይታወቅም።በምክትል ፕሬዝደንቱ መግለጫ መሠረት ከእስረኞቹ ሰላሳ-አምስቱ የፓርቲዉ የአመራር ባለሥልጣናት ናቸዉ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሰ