የምሥራቅ ኮንጎ ጥቃት
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 11 2007ማስታወቂያ
ባለፈዉ ዓርብ ለቅዳሜ አጥቢያ ብቻም ከሃያ የሚበልጡ ሰዎች አካላቸዉ ተቆራርጦ ተገድለዋል። ከዚህ ኢሰብዓዊ ድርጊት ጀርባ የተባበሩት የዲሞክራቲክ ኃይሎች የሚለዉን ስም የያዘዉ በእንግሊዝኛ ምህፃሩ ADF የተሰኘ በዩጋንዳን መንግሥት ላይ ያመፀዉ ቡድን እንዳለ ነዉ የሚገለጸዉ። የዶቼ ቬለዋ ማያ ብራዉን ይህን አስመልክታ ዓለም ዓቀፍ ቀዉስ የሚታይባቸዉ አካባቢዎችን አጥኚና መፍትሄ አፈላላጊ ቡድን ባልደረባን አነጋራለች። የበርሊን ዘጋቢያችን ይልማ ኃይለሚካኤል አጠናቅሮታል።
ይልማ ኃይለሚካኤል
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ