የማሊ መፈንቀለ መንግሥትና ተቃዉሞዉ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 18 2004ማስታወቂያ
የማሊን ፕሬዝዳት የአማዱ ቱማኒ ቱሬን መንግሥት አስወግደዉ ሥልጣን የያዙትን የጦር መኮንኖች የሐገሪቱ ሕዝብና ፖለቲከኞች ተቃወሟችዉ።የጦር ሁንታዉ ባስቸኳይ ሥልጣን እንዲለቅ የሐገሪቱ ሕዝብ በሰልፍ ሲጠይቅ፥ የሰላሳ ስምንት የፖለቲካ ማሕበራት ተጠሪዎች ደግሞ ለጦሩ ድጋፍ እንደሚይሰጡ አረጋግጠዋል።ሻምበል አማዱ ሳንጎ የመሯቸዉ የማሊ የመስመር መኮንኖች ያደረጉትን መፈንቅለ መንግሥት የተለያዩ መንግሥታትና ማሕበራት እያወገዙት ነዉ።የአፍሪቃ ሕብረት ማሊን ከአባልነት ሲያግድ፥ የአዉሮጳ ሕብረትና ዩናይትድ ስቴትስ ለማሊ የሚሰጡትን ምጣኔ ሐብታዊ ርዳታ አቁመዋል።የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሐይለ ሚካኤል ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።
ይልማ ሐይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ