1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሕዳር 22 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ኅዳር 22 2016

ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን በአርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች መግደሉን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ወነጀለ። ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች በወረዳው ሦስት መንደሮች በሁለት ቀናት በፈጸሟቸው ጥቃቶች በትንሹ 36 ሰዎች መገደላቸውን ሬውተርስ ዘግቧል።ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲያፈላልግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተቋቋመው ኮሚቴ የለያቸውን ሁለት የመጨረሻ እጩዎች ይፋ አደረገ። በሶማሊያ ላይ ተጥሎ የቆየው የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀብ እንዲነሳ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃው ምክር ቤት ሲወስን ሶማሌላንድ ተቃወመች። የቅዳሜ የዓለም ዐበይት ዜናዎችን ያድምጡ!

https://p.dw.com/p/4ZiFL
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።