ወባን የማጥፋት ጥረት
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 19 2002ማስታወቂያ
የዘንድሮዉን የወባ ቀን ምክንያት በማድረግ የተመ የህፃናት መርጃ ድርጅት UNICEF ይፋ ባደረገዉ መሰረት በዓለም ዙሪያ በወባ ምክንያት በየዓመቱ የ850,000 ሰዎች ህይወት እንደዋዛ ይቀጠፋል። በተለይ ይህ ጉዳት በአፍሪቃ ከሰሐራ በስተደቡብ በሚገኙ አገራት ይጠናል። ከተጠቀሰዉ ቁጥር ዘጠና በመቶዉ የሚከሰተዉ በዚሁ አካባቢ ነዉና። በኢትዮጵያ በድሬደዋና በጉራጌ ዞን አካባቢ ወባን መቆጣጠር ብሎም ለማጥፋት ከፍተኛ ተግባር ተከናዉኗል። ድሬደዋ ወባን ታሪክ አድርጌያለሁ ትላለች።
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ