1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኮሮና ለመከላከል የመገናኛ ብዙሀን ሚና 

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 1 2012

በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ስለ ኮሮና ቫይረስ ሰፊ ሽፋን እንደሚሰጡ አነቃቂም አስጠንቃቂም መልዕክቶች አሁንም አሁንም በስፋት ለህዝብ እያደረሱ መሆኑን አስተያየት ሰጭዎቹ ተናግረዋል። የመገናኛ ብዙሃኑ ዋጋና ኃይላቸው ከፍ ያለነው ያሉት አንድ የጋዜጠኝነት መምህር ደግሞ የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ከህዝቡ የተሻ እውቀት ሊኖርባቸዋል ይገባል ብለዋል።

https://p.dw.com/p/3ahqe
Äthiopien Addis Abeba | Mufti Haji Omar Idris, Präsident Islamic Affairs Supreme Council
ምስል DW/S. Muchie

ኮሮና ለመከላከል የመገናኛ ብዙሀን ሚና 

የኮሮና ተህዋሲ ወረርሽኝን ለመከላከል መገናኛ ብዙሃን ህዝብን በማስተማር ረገድ መልካም የሚባል ስራ ላይ መሆናቸውን ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸው ሰዎች ተናገሩ። በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ስለ ኮሮና ቫይረስ ሰፊ ሽፋን እንደሚሰጡ አነቃቂም አስጠንቃቂም መልዕክቶች አሁንም አሁንም በስፋት ለህዝብ እያደረሱ መሆኑን አስተያየት ሰጭዎቹ ተናግረዋል።ጊዜው የመገናኛ ብዙሃኑ ዋጋና ኃይላቸው ከፍ ያለበት ነው ያሉት አንድ የጋዜጠኝነት መምህር ደግሞ፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በጉዳዩ ላይ ያላቸው ግንዛቤ ውሱን በመሆኑ ራሳቸውን ከህዝቡ አንድ እርምጃ ማስቀደም ይኖርባቸዋል ሲሉም አሳስበዋል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ተጨማሪ ዘገባ አሰናድቷል።
ሰሎሞን ሙጬ 
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ