ከአዲስ አበባ ጅቡቲ የባቡር መስመር ግንባታ
ሐሙስ፣ መስከረም 19 2009ማስታወቂያ
ከአዲስ አበባዉ የፉሪ ለቡ የባቡር ጣቢያ እከ ደቡብ ወልደያ ያለዉ የባቡር መስመር ግንባታ ዘጠና ዘጠኝ በመቶ መጠናቀቁ ተሰምቷል። የኢትዮጵያን የኤኮኖሚ እድገት ያፋጥናል ከጎረቤት ሃገራት ጋር ያላትንም ትስስር ያጠናክራል የተባለለትን 656 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለዉን የአዲስ አበባ ጅቡቲ የባቡር መስመር ግንባታም ላለፉት አራት ዓመታት በመገንባት ላይ ይገኛል። ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ ይህ የባቡር መስመር ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ የመጎብኘት አጋጣሚዉን አግኝቶ ነበር፤ ለዛሬዉ የኤኮኖሚዉ ዓለም ጥንቅር ልኮልናል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ሸዋዬ ለገሠ