ከምስራቅ ወለጋ ሸሽተው አዲስ አበባ የተጠለሉ ተፈናቃዮች
ረቡዕ፣ ጥር 18 2014ማስታወቂያ
እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ጦር ብሎ የሚጠራዉ ሸማቂ ቡድን ጥቃት ያደርስብናል ብለዉ ከምስራቅ ወለጋ የሸሹ 107 ነዋሪዎች አዲስ አበባ እስጢፋኖስ ቤተ-ክርስቲያን ተጠልለዋል። ከተፈናቃዮቹ 30 ሕፃናት ናቸዉ። የኢትዮጵያ መንግስት ኦነግ ሸኔ በሚል ስያሜ በአሸባሪነት የፈረጀዉ ሸማቂ ቡድን ታጣቂዎች ምዕራብ ኦሮሚያ ዉስጥ በተለያየ ጊዜ በሰላማዊ ሰዎች ላይ አደጋ እንደሚጥል በየጊዜዉ መዘገባችን አይዘነጋም። አዲስ አበባ የሰፈሩት ተፈናቃዮች እንደሚሉት በሕይወታቸዉና ንብረታቸዉ ላይ ያንዠበበዉን አደጋ መንግስት እንዲከላከልላቸዉ ለወረዳና ለዞን ባለስልጣናት አቤት ቢሉም ሰሚ አላገኙም። አዲስ አበባ ከገቡት ተፈናቃዮች የተወሰኑት የቤተሰቦቻቸዉ አባላት ያሉበትን ሥፍራና ሁኔታ እንደማያዉቁ ዐስታዉቀዋል።
ሰለሞን ሙጬ
ነጋሽ መሐመድ
እሸቴ በቀለ